





የላንፍሮ ወረዳ አስተዳደር መልክት
የላንፍሮ ወረዳ አስተዳደር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በስልጤ ዞን ከሚገኙ 10 ወረዳዎችና 05 ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን ወረዳው በለውጥ ጎዳና ውስጥ ከሚገኙ የዞኑ ወረዳዎች አንዱ ነው፡፡የወረዳው መቀመጫ ጦራ ከተማ ሲሆን ከዞኑ ዋና ከተማ ወራቤ በስተ ምስራቅ አቅጣጫ 39 ኪሎሜትር ርቀት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ ከተማ ሆሳዕና በስተ ሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ 99 ኪ.ሜ እንዲሁም ከአዲስ አበባ በስተደቡብ አቅጣጫ 182 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ወረዳው በ18 ቀበሌዎችና በሁላት ታዳጊ ማዘጋጃ ቤታዊ ከተማ የተዋቀረች ሲሆን በወረዳዋ ከ……. በላይ የሚጠጋ የህዝብ ብዛት አለት። በወረዳው የሚገኘው አብዛኛው የማህበረሰብ ክፍል የእስልምና እምነት ተከታይ ሲሆን የስልጥኛ ቋንቋ ተናጋሪ ነው።በወረዳው የሚገኘው ማህበረሰብ አብዛኛው የእስልምና እምነት ተከታይ ይሁን እንጂ የተለያዩ ብሔርና ሃይማኖት ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በሰላምና በፍቅር ተዋደውና ተከባብረው በጋራ የሚኖሩበት፤የአብሮነትና የአንድነት መገለጫም ነው ወረዳው።
በተለይም ወረዳዉን አቋርጦ የሚያልፈው ከቆሼ-ጦራ-ሚቶ-ወራቤ የአስፋልት መንገድ ተጠቃሚ መሆን መጀመር ወረዳው ቀድሞውንም ከነበረው ለኑሮ፣ለንግድና ኢንቨስትመንት ምቹና በባህሪው ሞቅ ያለ የህዝብና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተደምሮ የወረዳውን ሁለንተናዊ ለውጥ ወደ ላቀ ደረጃ እንዲሸጋገር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሲሆን ይህም ወረዳው በሁሉም ዘርፍ ፈጣንና አስተማማኝ መዋቅራዊ ኢኮነሚያዊ ዕድገት እያስመዘገበ በፈጣን ዕድገት መገስገስ እንድችል ትልቅ አቀም መፍጠር ችሏል፡፡
